ስለ ቅዱስ ቁርባን
"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ!" (ማቴ 3: 1-2)
ተከታታይ ትምህርትና ለጥያቄዎት ምላሽ ለማግኘት ቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ
ስለ ቅዱስ ቁርባን
ምስጢረ ቅዱስ ቁርባን
ስለ ቅዱስ ቁርባን
ምስጢረ ቅዱስ ቁርባን
ተከታታይ ትምህርትና ለጥያቄዎት ምላሽ ለማግኘት ቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ
“ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።” (ዮሐ 6፡51)
ሰሞኑን በቴሌግራም ግሩፓችን የተነሱ ጥያቄዎች
ስጋ ደሙን ከመቀበል በፊት አንድ ክርስቲያን ማሟላት ወይም ማድረግ ያለበት ነገር፦
1/ የንሰሓ አባትቱን በማነጋገር ኀጢአት ካለ ንስሓ መግባት፣
2/ በስጋ ደሙ ከተወሰኑ በኋላ ወደ ኋላ መመለስ አይቻልምና ከቤተሰብዎም ይሁን ከማህበራዊ ኑሮ የሚያገናኙና የሚያጨቃጭቁ ቂም በቀል የሚያመጡ ሃሳቦች እንዳይኖሩ በተቻለ መጠን ሁሉንም ነገር ከመቁረብ በፊት ማስተካከል፣
3/ የተቀየምነው የተቀየመን፣ ያስቀየምነው ያስቀየመን፣ የተጣላነው የተጣላን ማንኛውም ሰው ካለ በንስሓ አባት ወይም በሽማግሌ አማካኝነት ይቅርታ ጠይቆ ቂም በቀልን መተዉ፣
4/ በግል ህይወታችን ሁል ግዜ በቋሚነት የምንጸልየው የጸሎት ፕሮግራም ለኖረን ያሰፈልጋል። ሰይጣን እንዳይዋጋንና በቅዱስ ቁርባን ያገኘነውን በረከት እንዳያሳጣን የምንቋቋምበት መንፈሳዊ ተጋድሎ በጸሎት ስለሆነ ነው፣
5/ ለመቁረብ ሁሉን ነገር አሳክተን ከወሰንን በኋላ ከምንቆርብ 3 ቀን በፊት ወንድ ይሁን ሴት ቤተሰብ ካለ ከግንኙነት (ፆታዊ ግንኙነት) መቆጠብ ያስፈልጋል።
6/ በሰጋ ወደሙ አንድ ሰው ተወሰነ ማለት እንደ ቤተክርስቲያን ስርአት ፈጽሞ ከአለማዊ ጠባይ ወጣ ማለት ስለሆነ በተቻለ መጠን አቀሙ የሚችለውን የበጎ ስራና የርህራሄ ስራ መስራት፣ ቅዱስ ቁርባን በበጎ ስራ መገለጽ ስላለበት ለድኆች ርህራሄ ማድረግ፣ ጠቃሚ የሆኑ መንፈሳዊ ስራ ላይ መሳተፍ፣
እነዚህ ከላይ የጠቀስናቸው ሁሉ ለቅዱስ ቁርባን የምንበቃባቸው ከአንድ ክርስቲያን የሚጠበቁ መልካም እሴቶች ናቸዉ።
በተጨማሪም ለቅዱስ ቁርባን በምንቀርብበት ግዜ የምንለብሰው ልብሳችን ለዚህ ብቻ ተብሎ የተዘጋጀ መንፈሳዊነትን ሊገልጽ የሚችል ራሱን የቻለ ልብስ ሊኖረን ይገባል። ንጹሕ ባሕርይ እግዚአብሔር ንጹሕ ነገርን ይወዳልና። በአለም ላይ ስንኖር በአለም ራሳችንን ለመግለጥ ልዩና ውድ ልብስ የምንገዛ ከሆነ ከዚህ በላይ በከበረው በእግዚአብሔር ጉባኤ ራሱን የቻለ ልብስ ቢኖረን፤ ባይኖረን እንኳ ያንኑ ልብሳችንን በጽዳት ልንይዘው ይገባል። አንፃራዊ ትርጓሜው በልብሱ አንፃር ውስጣችንንም ንጹሕ አድርገን ቀርበናል አንተም ንጹሕ ባሕርይ አምላክ ነህ ለማለት ነው።
ሴትም ሆነ ወንድ በሱባኤ እያለ እንዲህ አይነት ፈተና ቢገጥመው ፈተናው ባጋጠመው እለት የሱባኤውን ጋብ ፈጥሮ ሱባኤውን እንደገና በሚቀጥለው እለት መፈጸም ይችላል። ኢሄ ካጋጠመው ከ 3 ቀን በኋላ ቁርባንም መቁረብ ይችላል። ነገር ግን ይህ የሚሆነው በህልም እርኩስ መንፈስ ለፈተነው እንጂ ራሱ አስቦት የፈጸመው ዝሙት ካለ ግን እንደገና ለንስሓ አባቱ ተናዞ ባለፈዉ ከተሰጠው ንስሓ በላይ በእጥፍ ቀኖና መቀበል እንዳለበት የቤተክርስቲያን ስርዓት ያዛል።
ጠያቂያችን እንዳሉት ሲቆርቡ ኑረው በመካከል ወደ ቅዱስ ቁርባን የማያቀርብ ነውር ካጋጠማቸው ወይም ደግሞ በኀጢአት ከተሰናከሉ ለጊዜው መቁረባቸውን አቁመው ወደ ንስሓ አባታቸው ቀርበው የፈጸሙትን በደል ከተናዘዙ እና ንስሓቸውን ከጨረሱ በኋላ መቁረባቸውን መቀጠል ይችላሉ። ነገር ገን ጥፋቱን በመደጋገም ሁል ጊዜ በንስሓ እመለሳለሁ በሚል መንፈስ መሄድ እንደሌለባቸው የቤተክርስቲያን ቀኖና ይደነግጋል። ዋናው ቁም ነገር ማንኛውም ክርስቲያን በምንም ይሁን በምን ከቅዱስ ቁርባን ላለመለየት በየጊዜው መንፈሳዊ አላማውን በማጽናት መታገል እንዳለበት እንመክራለን።
ቅዱስ ቁርባን የሚቀበል ማንኛውም ሰው ለንስሐ አባቱ መናገር ያለበት ራሱ የሚያውቀው ጥፋት ከሌለበት በስተቀር ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል በተዘጋጀ ቁጥር መናገር አይጠበቅበትምና ይህንን የጠየቁን አባላችን በዚህ ጉዳይ ላይ የሚያሳስብዎት ነገር የለም።
ተከታታይ ትምህርትና ለጥያቄዎት ምላሽ ለማግኘት ቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ